የአፍሪቃ እግር ኳስ ዋንጫ፤ ያሸንፋሉ ተብለዉ የሚጠበቁ ቡድኖች
የስኬታማነት ስልት ለስኬታማ አሰልጣኝነት?
እንደ እቅዱ ቢሆን ኖሮ የጎርጎረሳዉያኑ 2015 ዓ,ም የአፍሪቃ ዋንጫ ግጥምያ የሚካሄደዉ በሞሮኮ ነበር። ተነሳ የተባለዉን የኤቦላ ወረርሽኝ ተከትሎ ሞሮኮ፤ ጨዋታዉን ማስተናገድ ባለመፈለግዋ ግጥምያዉ በኢኳቶሪያል ጊኒ ተካሂዶአል። የሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን ግን በጫወታዉ እንዳይሳተፍ ታግዶ ነበር። ዘንድሮ ግን አዚዝ ቦሃዱዝ «ግራ» እና ባልደረቦቹ ጋቦን በሚካሄደዉ ግጥምያ ሜዳ የኳስ ጨዋታ ማለት እንዴት እንደሆነ ማሳየት ይፈልጋሉ። አሰልጣኝ ሃርቨ ሬንአርድ በዚህ አይታሙም፤ ምክንያቱም በጎርጎረሳዊዉ 2012 ዓ.ም የዛምቢያ አሰልጣኝ ነበሩ፤ በ2015 ደግሞ ኮት ዲቯርን ለዋንጫ አብቅቷል።
አዘጋጅ: አዜብ ታደሰ